måndag 8 november 2010

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያ


የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ከአምስቱ የኦርየንታል (ምስራቃዊ) ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክሪስቲያናት አንዱ ነው። ኢትዮጵያ ክርስትና እምነት ከተቀበለችበት 4ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ እስከ ጥር ቀን ፲፱፻፵፫ . (1951 ...) ድረስ የእስክንድርያ ኮፕት ቤተ ክርስቲያን ክፍል ነበር። በ፲፱፻፵፫ . ግን የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ባስልዮስ ከእስክንድርያው ፓትርያርክ አቡነ ዮሳብ 2 የጵጵስና ማዕረግ ተቀበሉ። ኢትዮጵያም፤ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ እራሷን የቻለች ሆነች። ወደ 40-45 ሚሊዮን የሚቀርቡ ምእመናን ሲኖሩት ከምሥራቃዊ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ትልቁ ነው
«ተዋሕዶ» ልሣነ ግእዝ የመነጨ ቃል ሲሆን፡ ትርጒሙም «አንድ ሆኖ» ማለት ነው። ለዚሁም ዐረብኛ ተመሳሳይ ቃል «ታውሒድ» ሲባል በአንድ አምላክ ብቻ ማመን የሚለውን ፅንሰ ሀሳብ ያመለክታል። ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስትያናት ቃሉ የሚነካ የክርስቶስ ባሕርይ «ሰብዓዊ» እና «መለኮታዊ» ተለይቶ ሳይሆን አንድ ብቻ እንደሆነ የሚለው ጽኑ እምነት ነው።